ሸንጎ ህጉን ይደግፋል፤ ለተፈጻሚነቱም ተግቶ
ይፋለማል
HR 128 ተብሎ የሚታወቀው ባሜሪካ ኮንግረስ (ፓርላማ ) ውስጥ ለውሳኔ ቀርቦ የነበረው በኢትዮጵያ
መንግስት የመብት አያያዝ ላይ ያተኮረ የህግ ረቂቅ እነሆ ትናንት መጽደቁ ተነገረ። በውጭ አገር ያሉ
የሰብዓዊ መበት ተከራካሪዎችና የተደራጁ ኢትዮጵያውያን ይህ የህግ ረቂቅ እንዲጸድቅና በስራ ላይ
እንዲውል ለረጅም ጊዜ ከፍተኛ ተጋድሎ ሲያድርጉ ቆይተዋል። ሸንጎ ለዚህ ስኬት ታጥቀው ለታገሉ
ሃይሎች በሙሉ ያለውን አድናቆትና ክብር እያስታወቀ፤ የረቂቁ ህግ ሆኖ መጽደቅ ለኢትዮጵያ ህዝበና
ለመላው የዴሞክራሲ ሃይሎች ታላቅ ድል መሆኑን ይገልጻል።HR 128