Quantcast
Channel: General – Addis Dimts Radio
Viewing all 96 articles
Browse latest View live

Radio Show For June 12/2016

$
0
0

According to the Office of the UN High Commissioner for Human Rights (OHCHR),

“Eritrea is an authoritarian State. There is no independent judiciary, no national assembly and there are no other democratic institutions in Eritrea. This has created a governance and rule of law vacuum, resulting in a climate of impunity for crimes against humanity to be perpetrated over a quarter of a century

But Mr. Neamin Zeleke, Head of Foreign Affairs of Patriotic Ginbot 7 Says That is Not True.

Meanwhile Mr. Yared Hailemariam Association For Ethiopian Human Rights Disagree
Liste the Interview


በስደት የሚገኘው ሕጋዊው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ፓትሪያሪክ አቡነ መርቆሬዎስ በሚገኙበት ነገ በካሊፎርኒያ በኦክላንድ መካነ ሰላም መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን አዲስ ኤጲስ ቆጶሳትን ይፋ ያደርጋል::

$
0
0

በስደት የሚገኘው ሕጋዊው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን  ፓትሪያሪክ አቡነ መርቆሬዎስ በሚገኙበት ነገ  በካሊፎርኒያ በኦክላንድ መካነ ሰላም መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን አዲስ  ኤጲስ ቆጶሳትን   ይፋ ያደርጋል::

አዲስ የተሾሙት ኢጲስ ቆጶሳት የጵጵስና ስማቸው ማን እንደሚሆን እና የት ሃገረ ስብከት እንደሚሾሙ ለጊዜው አልተገጽም::

1ኛ. የአባ ወልደ ትንሣኤ አያልነህ አጭር የሕይወት ታሪክ

አባ ወልደ ትንሣኤ

አባ ወልደ ትንሣኤ

አባ ወልደ ትንሣኤ አያልነህ ከአባታቸው አቶ አያልነህ ጌጡ እና ከወይዘሮ ማንአህሎሽ ተበጀ በኢትዮጵያ ምድር በ1954 ዓ.ም ተወለዱ ። እድሜያቸው ለትምህርት እንደ ደረሰ በአካባቢው ከነበሩት የዜማ መምህር ከመሪጌታ ዲበ ኩሉ ዘንድ ተልከው ከፊደል እስከ ጸዋትወ ዜማ ተምረዋል ። የቅዳሴ ዜማ ከመምህር አባ ወልደ ትንሣኤ ጥሩነህ ፣እንዲሁም በጎጃም ክፍለ ሀገር በደምበጫ ወረዳ በብር ሸለቆ በደብረ ገነት መድኃኔ ዓለም ገዳም ከየኔታ ተክለ ጽድቅ ተምረዋል ። ቅኔ ለመማር ባላቸው ጉጉት የተነሣ ወደ ጎንደር ክፍለ ሀገር ደራ ወረዳ ዛራ ሚካኤል በመሄድ ፥ ብዙ ደቀ መዛሙርትን በማፍራታቸው ከሚታወቁት ከየኔታ ጥበቡ ባየ ቅኔ ከነአገባቡ ተምረዋል ። እንዲሁም ወደ ባሕር ዳር ከተማ በመጓዝ ከየኔታ መንግሥቱና ኋላም በዝዋይ ሐመረ ኖኅ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም የቅኔ መምህር ከነበሩት ከመምህር አበበ ምሥጢር አደላድለዋል ።

በዘመናዊ ትምህርትም የአንደኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በጎንደር ክፍለ ሀገር እንፍራዝ ከተማ እንፍራዝ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ፥ የመለስተኛና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በጎንደር ከተማ በፋሲለደስ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተምረው አጠናቅቀዋል ።

ስብከተ ወንጌልን በዘመናዊ መንገድ ለማቅረብ ከነበራቸው ጉጉት የተነሣ ፥ የስብከት ዘዴን ፥ የቤተ ክርስቲያን ታሪክንና ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያንን ለመማር ፥ በሸዋ ክፍለ ሀገር በሚገኘው የዝዋይ ካህናት ማሠልጠኛ በመግባት በዚያ የሚሰጠውን መንፈሳዊ ሥርዓተ ትምህርት ተከታትለው በመዐርግ ተመርቀዋል ።

በመቀጠልም በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኘው በሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ ከፍተኛ መንፈሳዊ ትምህርት ቤት ገብተው ለአራት ዓመታት የሚሰጠውን የነገረ መለኮት ትምህርትና የስብከት ዘዴ ተከታትለው በዲፕሎማ ተመርቀዋል ።

የአሁኑ ብፁዕ አቡነ እንድርያስ የቀድሞው አባ ጎሃ ጽባሕ የመጻሕፍትን ምሥጢር እንደ ገለጹላቸው ፥ በምክራቸውም እንዳነጿቸውና እንዳስተማሯቸው ፥ ከዚያም አልፎ ለአሁኑ ሕይወታቸው መሠረት እንደ ጣሉላቸው ይመሰክራሉ ።

አባ ወልደ ትንሣኤ አያልነህ መዐርገ ዲቁና ፥ በወቅቱ የጎንደር ክፍለ ሀገር ሊቀ ጳጳስ ከነበሩት ከብፁዕ አቡነ እንድርያስ በ1964 ዓ.ም ተቀብለዋል ። በመቀጠልም እንደ ኢትዮጵያ አቈጣጠር በ1978 ዓ/ም በጊዜው አሰብ ራስ ገዝ ተብሎ ይጠራ በነበረው ክፍለ ሀገር በአሰብ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ከብፁዕ አቡነ በርናባስ መዐርገ ምንኩስናና ቅስና ተቀብለዋል ።

በአሰብ ራስ ገዝ በብፁዕ አቡነ በርናባስ ሥር በቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን የስብከተ ወንጌል ኃላፊና ሰባኬ ወንጌል በመሆን ሰፊ አገልግሎት አበርክተዋል ። በመቀጠልም ወደ አዲስ አበባ በመምጣት ፥ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሥር ተመድበው በተንቀሳቃሽ ሰባኪነት አገልግለዋል ። አባ ወልደ ትንሣኤ አያልነህ ፥ ሕይወታቸውን ለወንጌል አገልግሎት የሰጡ ፥ ታላቁንም ታናሹንም በትሕትና የሚያገለግሉ ፥ ቃላቸው ከግብራቸው የተስማማላቸው ፥ የሚኖሩትን የሚሰብኩ ፥ የሰበኩትን የሚኖሩ አባት ናቸው ። ይህም ሊታወቅ ፥ ስንቶች በሙስና የሚዋደቁለትን ሹመት ማለትም በአዲስ አበባ የቦሌ የኮተቤና የየካ አውራጃዎች ሊቀ ካህናት ይሁኑ ተብለው ሲሾሙ ፥ የኔ መዐርግ ወንጌል ናት ብለው በብዙ መከራ ውስጥ ወንጌልን የሰበኩ አባት ናቸው ።

በሚሊዮኖች የሚቈጠሩ ምእመናንን በሚስበው የስብከት አቀራረባቸው ፥ በቤተ ክርስቲያናችን ዘመናዊ ታሪክ ውስጥ ፥ ለዘመናዊ የስብከት ዘዴ ፋና ወጊ ተብለው ከሚጠቀሱት አባቶች አንዱ ናቸው ። በስብከታቸውም ብዙዎችን ለቅዱስ ቍርባን አብቅተዋል ። ብዙዎችን ከተሳሳተ መንገድና ትምህርት መልሰዋል ። እግዚአብሔር ለዚህ ዘመን ተስማሚ አድርጎ በሰጣቸው አንደበታቸው ከአህጉር አህጉር እየተንቀሳቀሱ መጽናናት ለሚያስፈልገውና ፥ ወንጌልን ለተጠማው ሕዝበ ክርስቲያን የወንጌልን ቃል በትሕትናና በቆራጥነት በመዝራት የብዙዎችን ልቦና አለምልመዋል ።

የመንግሥትን ለውጥ ተከትሎ በአገር ውስጥ ያለው የቤተ ክርስቲያኒቱ ሁኔታ ለወንጌል አገልግሎት አመች አልሆን ሲላቸው ከሀገራቸው ተሰደው ወደ አሜሪካ ተጉዘው በሎስ አንጀለስ ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን በሰባኬ ወንጌልነት ተመድበው በማገልገል ዕለት ዕለት የሚያስተምሩትም ትምህርት እየተቀረጸ በሀገር ቤትና በመላው ዓለም በምትገኘዋ ቤተክርስቲያን እየተሰራጨ ትምህርታቸው ለአያሌ ኦርቶዶክሳውያን ወንድሞችና እኅቶች መጽናኛና መማሪያ ብሎም በስሕተት ትምህርት ላሉት ሁሉ መልስ መስጫ በመሆን አገልግሎአል ።

አባ ወልደ ትንሣኤ አያልነህ በአሁኑ ወቅት ፥ በመላው ዓለም በመዘዋወር ፥ በአሜሪካ፥ በካናዳ ፥ በአውሮፓ፥ በአፍሪካ ፥ በኒውዚላንድና በአውስትራሊያ እየተዘዋወሩ በማገልገል ላይ ይገኛሉ ። በዚህም አገልግሎታቸው ፥ አብያተ ክርስቲያናት በወንጌል እንዲታነጹ እንዲጽናኑ አድርገዋል ። አባ ወልደ ትንሣኤ ሕይወታቸውን ለወንጌል አገልግሎት የሰጡ አባት በመሆናቸው ፥ ሕጋዊው ቅዱስ ሲኖዶስ በምልዐተ ጉባኤው «ሐዲስ ሐዋርያ» በሚል ለቤተ ክርስቲያን የሰጡትን አገልግሎትና ድካማቸውን የሚገልጥ ስም ሰጥቶአቸዋል ።

ይህን መንፈሳዊ አገልግሎታቸውን በመመልከት ፥ በማኅበረ ካህናቱ ፥ በማኅበረ ምእመናኑ እንዲሁም በሰንበት ትምህርት ቤት ተማሪዎች ተጠቁመውና ተመርጠው ፥ በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ለከፍተኛው የቤተ ክርስቲያን መዐርገ ክህነት ለኤጲስ ቆጶስነት ተመርጠዋል ።

2ኛ. አባ ጽጌ ድንግል ደገፋው አጭር የሕይወት ታሪክ

 አባ ጽጌ ድንግል ደገፋው

አባ ጽጌ ድንግል ደገፋው

አባ ጽጌ ድንግል ደገፋው ከአባታቸው ከአቶ ደገፋው ዓለሙና ከእናታቸው ከወይዘሮ አየሁ ተመስገን ኅዳር 27 ቀን 1958 ዓ.ም በኢትዮጵያ ተወለዱ ። አባ ጽጌ ድንግል ደገፋው እድሜአቸው ለትምህርት እንደ ደረሰ ፥ በተወለዱበት አካባቢ በሚገኘው “ደብረ ኢየሱስ” ተብሎ በሚጠራው ታላቅ ገዳም ከሚገኙት የአብነት መምህራን ከመሪጌታ ዓለሙ ተገኘና ፥ ከመሪጌታ ርኁቀ መዓት ተፈራ ፥ ከፊደል እስከ ጸዋትወ ዜማ ያለውን የቤተ ክርስቲያን ትምህርት በሚገባ ተምረው ካጠናቀቁ በኋላ የዲቁናን መዐርግ ከብፁዕ አቡነ ማርቆስ እጅ በ1970 ዓ.ም ተቀብለዋል ።
አባ ጽጌ ድንግል ኢትዮጵያ በሚገኘው በታላቁና ጥንታዊ ገዳም (ናዝሬት ኢየሱስ ገዳም) አገልግሎት ሲሰጡ ከቆዩ በኋላ ወደ ቅኔ ትምህርት ቤት በመሄድ በመጀመሪያ በመንግሥቶ ኪዳነ ምሕረት ከመሪጌታ ደጉ ፥ ከዚያም ወደ ቀራንዮ መድኃኔ ዓለም በመሄድ ከመሪጌታ ተስፋ ፥ እንዲሁም በደንበጫ ቅዱስ ሚካኤል ከመሪጌታ ብዙአየሁ ቅኔ ተምረዋል ። አገባቡን በሚገባ ለማሄድና ምሥጢር ለማደላደል ወደ ደብረ ወርቅ በመሄድ ከመሪጌታ ከብካብ ፥ በይጥባቆ ቅዱስ ሚካኤል ከመሪጌታ ዳንኤል ቅኔውን ከነአገባቡ አጠናቀው ተምረዋል ። የቅኔ ትምህርታቸውን እንዳጠናቀቁም ወደ ታላቁ ገዳም በመመለስ በገዳሙ ሥርዓት መሠረት አበው መነኮሳትን በመታዘዝና በገዳሙ ሥርዓት መሠረት አስፈላጊውን አገልግሎት በመስጠት ከቆዩ በኋላ ፥ በብፁዕ አቡነ መቃርዮስ እጅ በ1975 ዓ.ም ሥርዓተ ምንኩስናና የቅስና መዐርግ በተወለዱ በ17 ዓመታቸው ተቀብለው በገዳሙ ለሁለት ዓመታት አገልግለዋል ።

አባ ጽጌ ድንግል ወደ ዲማ ጊዮርጊስ በመሄድ የአዲስ ኪዳን ትርጓሜን ከታላቁና ታዋቂ ከሆኑት መምህር ከመምህር ማርቆስ ፣ እንዲሁም የውዳሴ ማርያምንና የቅዳሴ ማርያምን ትርጓሜ ከመምህር ዲሜጥሮስ ተምረዋል ። ወደ አዲስ አበባ በመምጣት ፥ ከደገኛው አባት ከብፁዕ አቡነ ዜና ማርቆስ ዘንድ ለጥቂት ጊዜ ከተቀመጡ በኋላ ፥ ወደ ዝዋይ ገዳም በመሄድ ገዳሙን እንዲያገለግሉና በገዳሙ ከሚገኘው የካህናት ማሠልጠኛ ትምህርት ቤት የሚሰጠውን ትምህርት እንዲከታተሉ ወደ ዝዋይ ተላኩ ። በማሠልጠኛው የሚሰጠውን ትምህርት ተከታትለው ፥ ከ63 ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን መካከል በአንደኛ ደረጃ በመዐርግ ተመርቀዋል ። ከመምህር ዘሚካኤል የመዘገበ ቅዳሴን ትምህርት በሚገባ ተምረው እንደ ጨረሱ ለሦስት ዓመታት ያህል በዝዋይ ገዳም አገልግሎት ሰጥተዋል ።

አባ ጽጌ ድንግል ከእነዚህ ታላላቅ መምህራን የቀሰሙትን ዕውቀት በተግባር ላይ በማዋልም ፥ በብፁዕ አቡነ ዜና ማርቆስ መልካም ፈቃድ በወለጋ ክፍለ ሀገር ነቀምት ከተማ በሚገኙት በመካነ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን በቅስና እና በአስተዳዳሪነት ፣ በደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን በአስተዳዳሪነት ከመስከረም ወር 1979 ዓ.ም.እስከ ጥር ወር 1982 ዓ.ም.አገልግለዋል ። በእነዚህም ዓመታት ሁሉንም በሰላም በፍቅርና በአንድነት በመያዝ እንዲሁም ታላላቅ ሥራዎችን በመሥራትና በማሠራት ለአብያተ ክርስቲያናት እድገትና ሰላም ፥ ለወንጌል አገልግሎት መስፋፋት ቅድሚያ በመስጠት በትጋት በታማኝነትና በቅንነት አገልግለዋል ። በተለይም በነቀምት ከተማ በምትገኘው በርእሰ አድባራት ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን በዋና አስተዳዳሪነት ባገለገሉበት ዘመን በታሪክ የሚመዘገቡና በምሳሌነት የሚጠቀሱ ቋሚ ሥራዎችን እንዲሠሩ በማድረግ ታላቅ አገልግሎት አበርክተዋል። በመቀጠልም ወደ አዲስ አበባ በመምጣት ፥ በቅዱስ ዮሴፍ ቤተ ክርስቲያን የስብከተ ወንጌል ኃላፊ በመሆን በደብሩ ቋሚ የስብከተ ወንጌል ፕሮግራም እንድቋቋም አድርገዋል።

በመቀጠልም የደብረ ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ ሁነው በማገልገል ላይ ሳሉ በ1985 ዓ ም በጥር ወር በምዕራቡ ዓለም የምትገኘውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ባላቸው እውቀትና ሙያ እንዲያገለግሉ ከአምስት መነኮሳት ጋር ወደ ውጭ አገር ተላኩ ። አባ ጽጌ ድንገል ደገፋው በተላኩበት መሠረት የተሰጣቸውን አደራ ለመወጣት በካሪቢያን ደሴቶችና በሰሜን አሜሪካ በሚገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አብያተ ክርስቲያናት በመዘዋወር ለሁለት ዓመታት ያህል ሐዋርያዊ ተልእኮአቸውን ለመወጣት ከፍተኛ አገልግሎትን አበርክተዋል ። በዚህም ወቅት፥ አባት ከማጣት የተነሣ የተበተኑትን ሰብስበዋል ፥ የአካባቢው ተወላጆች የሆኑትን አስተምረው አጥምቀዋል ።

በመቀጠልም በአሜሪካ ወደ ሎስ አንጀለስ ቅድስት ማርያም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በመምጣት ቤተ ክርስቲያኒቱን ላለፉት 22 ዓመታት ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ በትጋት አገልግለዋል ። በዋናነት ከሚያገለግሏት የቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ባሻገር አገልጋይ ካህናት
በሌሉበት ቦታዎችና አብያተ ክርስቲያት ባልተቋቋመባቸው ቦታዎች አብያተ ክርስቲያናት እንዲቋቋሙ በማድረግና የወንጌል አገልግሎትን በማስፋፋት በውጭ ዓለም በአሜሪካ ለሚገኙ ኢትዮጵያውያን ከፍተኛ አገልግሎት ያበረከቱ ታላቅ ሐዋርያ ናቸው ።

እንዲሁም ከሃያ አምስት ዓመታት በላይ በአስተዳደር ልዩነት የቆየችውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አንድ ለማድረግ በተጀመረው የሰላምና አንድነት ጉዞ ላለፉት ሁለት ዓመታት የሰላም ሐዋርያ በመሆን ከሚጥሩ አባቶች ጋር በመሰለፍ ያደረጉትን ከፍተኛ ጥረት ታሪክና ትውልድ የማይረሳው ነው ።

በዘመናዊ ትምህርት ራሳቸውን አዘጋጅተው ትውልዱን ለማገልገል ባላቸው ከፍተኛ ፍላጎት መሠረት ፥ በአገር ውስጥ የአንደኛ ደረጃ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን ካጠናቀቁ በኋላ ፥ የመጀመሪያ ድግሪያቸውን ከካሊፎርንያ እስቴት ዩኒቨርስቲ ኖርዝ ሪጅ በማኅበራዊ ጥናትና በቢዝነስ አስተዳደር (B.A.Degree in Sociology and Business Administration) ሁለተኛ ድግሪያቸውን ከካሊፎርኒያ ዩኒቨርስቲ ደሚንገዝ ሂልስ በማኅበራዊ ጥናት ማስተር (M.A.Degree inSociology) እንደ ገና በካሊፎርንያ ዩኒቨርስቲ እርቫይን በክሊኒካል ሳይኮሎጂ ማስተር ድግሪ (M.A. Degree in Clinical Psychology) የማስተርስ ድግሪ ተመርቀዋል ። በአሁኑ ሰዓት የመጨረሻ ድግሪያቸውን ለመያዝ በካሊፎርንያ ዩኒቨርስቲ እርቫይን የዶክትሬት ድግሪያቸውን በክሊኒካል ሳይኮሎጂ (Ph.D. in Clinical Psychology) የመመረቂያ ጥናታቸውን በመሥራት ላይ ይገኛሉ ።

በውጭ ዓለም በሕጋዊ ቅዱስ ሲኖዶስ መንፈሳዊ አመራር ሥር ላለቺው ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ፣ አባ ጽጌ ድንግል ደገፋው ባላቸው የአስተዳደርና የአመራር ችሎታ ፥ እንዲሁም መፈሳዊና ዘመናዊ እውቀት የመጀመሪያው የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ሁነው በመሾም በስደት ያለችውን ቤተ ክርስቲያን ለማደራጀትና በታማኝነት ለማገልገል ከፍተኛ ኃላፊነትን ተቀብለው ፣ የጠቅላይ ቤተ ክህነቱን የአስተዳደርና የመምሪያ ኃላፊዎችን በማቋቋምና በመሥራት ላይ ይገኛሉ ። በዚህም አግልግሎታቸው ወቅት የመንበረ ፓትርያርክ ጽ/ቤቱ በዋሽንግተን ዲ.ሲ. እንዲገዛ ፤ ሕጋዊው ቅዱስ ሲኖዶስ የሚመራበት ሕገ ቤተ ክርስቲያን እንዲዘጋጅና የተለያዩ የመምሪያ ኃላፊዎች እንዲቋቋሙና የተደራጀ ሥራ እንዲሠራ በማድረግ ከፍተኛ አስተዋጽዖ ያደረጉ ታላቅ አባት ናቸው ።

ይህን መንፈሳዊ አገልግሎታቸውን በማየት ፥ በማኅበረ ካህናቱ ፥ በማኅበረ ምእመናኑ እንዲሁም በሰንበት ትምህርት ቤት ተጠቁመውና ተመርጠው ፥ በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ለከፍተኛው የቤተ ክርስቲያን መዐርገ ክህነት ለኤጲስ ቆጶስነት ተመርጠዋል ።

3ኛ. የአባ ገብረ ሥላሴ ጥበቡ አጭር የሕይወት ታሪክ

አባ ገብረ ሥላሴ ጥበቡ

አባ ገብረ ሥላሴ ጥበቡ

አባ ገብረ ሥላሴ ጥበቡ በሰሜን ኢትዮጵያ መስከረም 30 1950 ዓ.ም ተወለዱ። እድሜያቸው ለትምህርት እንደ ደረሰ ፥ በተወለዱበት አካባቢ ፥ በታላቁ ደብር በጉና ሚካኤል ደብር ከመሪጌታ ገበየሁና ከልጃቸው መሪጌታ ሙሉጌታ መዝሙረ ዳዊትና የቃል ትምህርት ተምረዋል ።
በመቀጠልም ፥ መሪጌታ አክሊሉ እና መሪጌታ ከሃሊ ከተባሉ መምህራን ምዕራፍና ጾመ ድጓ ተምረዋል ። ለቅኔ ትምህርት ወደ ጎጃም በመሄድ ከመሪጌታ ተከሥተ ፣ ኋላም በዛራ ሚካኤል ከሚገኙት ከታላቁ ሊቅ ከመልአከ ምሕረት ጥበቡ ቅኔን ከነአገባቡ ተምረዋል ። ከቅኔ መምህራቸው ከመልአከ ምሕረት ጥበቡ ጋር ያላቸው ፍቅርና ቅርርብ ልዩ በመሆኑ ፥ “አባ ገብረ ሥላሴ ጥበቡ” ተብለው የሚጠሩት በዚህ ምክንያት ነው ።
የቅኔ ትምህርታቸውን እንዳጠናቀቁ ፥ አቋቋም ለመማር በነበራቸው ጽኑእ ፍላጎት መሠረት ፥ በጎንደር ዓየር ማረፊያ አጠገብ በምትገኘው በማርያም ደብር ከመሪጌታ ኤርምያስ ሞላ ፣ ጉቢያ ኢየሱስ ደግሞ ከመሪጌታ ልዑል ፥ እንዲሁም በዋውቻ ዮሐንስ ከመሪጌታ መዝገቡ በሚገባ ተምረዋል ።
አባ ገብረ ሥላሴ ጥበቡ ለስብከተ ወንጌልና የቅዱሳት መጻሕፍትን ዓለም ለመመርመር ከፍተኛ ፍቅር ስለ ነበራቸው ፥ ትርጓሜያቱን በሚገባ ለማሄድ ይመኙ ነበር። በመሆኑም ይህን ምኞታቸውን ፍጻሜ ለማድረስ ፥ የትርጓሜው ማዕከል ወደ ሆነው ወደ ጎንደር መንበረ መንግሥት መድኃኔ ዓለም በመምጣት ፥ ከታላቁ መምህር ከሊቀ ሊቃውንት መንክር መኮነን የመጻሕፍት ትርጓሜ ተምረዋል ።

ዘመናዊ ትምህርት ለመማር በነበራቸው ጉጉትም ፥ ከቤተ ክርስቲያኒቱ ትምህርት ጎን ለጎን ፥ የአንደኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በጎንደር ኅብረት እና ደብረ ሰላም ትምህርት ቤቶች ፤ የመለስተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በአዲስ አበባ ጳውሎስ ትምህርት ቤት ፣ የሁለተኛ
ደረጃ ትምህርታቸውን በጎንደር ፋሲለደስ ትምህርት ቤት ተከታትለዋል ።

የነገረ መለኮት ትምህርታቸውን በጥልቀት ለመከታተል በነበራቸው ጉጉት ፥ በአዲስ አበባ በሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ የነገረ መለኮት ሴሚናሪ በዲፕሎማ ተመርቀዋል ። ከአገር ከወጡ በኋላም በነገረ መለኮት ትምህርቱ እጅግ ታዋቂ በሆነውና በአሜሪካ በሚገኘው በቅዱስ ቭላድሚር የነገረ መለኮት ሴሚናሪ (St. Vladi- mir theological seminary የማስተርስ ኦፍ ዲቪኒቲ ድግሪያቸውን ። እንዲሁም ተጨማሪ የማስተርስ ድግሪያቸውን
በሃይማኖት ትምህርት በኒዮርክ ከሚገኝ ዩኒቨርስቲ አግኝተዋል ። በአትላንታ ጆርጂያ በሚገኘው የኢሞሪ ዩንቨርስቲ በክሊኒካል ፓስቶራል ኢጁኬሽን የምስክር ወረቀት አግኝተዋል ። በሳንፍራንሲስኮ ቴዎሎጂካል ሴሚናሪ የዶክትሬት ትምህርታቸውን ተከታትለዋል ።

አባ ገብረ ሥላሴ ጥበቡ መዐርገ ዲቁናን ከብፁዕ አቡነ ማርቆስ በደብረ ማርቆስ ከተማ በ1966 ዓ ም ። መዐርገ ቅስና ደግሞ ፥ በታላቁ ገዳም በደብረ ሊባኖስ ከብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ በ1983 ዓ ም ተቀብለዋል ።

አባ ገብረ ሥላሴ ጥበቡ ፥ ከልጅነት እስከ እውቀት በገበዩት ሰፊ የሆነ የትምህርትና የሥራ ልምድ ቤተ ክርስቲያንን በብዙ አገልግለዋል ። ከእነዚህም መካከል በኢትዮጵያ 1ኛ/ በአዲስ አበባ የወልደ ነጎድጓድ ዮሐንስ ቤተ ክርስቲያን የሰንበት ትምህርት ቤት አስተማሪ ፤ 2ኛ/ የጎንደር ሀገረ ስብከት የስብከተ ወንጌልና የሰንበት ምህርት ቤቶች ክፍል ኃላፊ ፤ 3ኛ/ የሰሜን ጎንደር ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ ፤ የምዕራብ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ ሁነው አገልግለዋል ።

ወደ አሜሪካ ከመጡ በኋላም በአሜሪካ በሚገኙ የተለያዩ አብያተ ክርስቲያናት ማለትም በኒውዮርክ ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን በዋና ካህንነት ፤ በሲያትል መካነ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን በሰባኬ ወንጌልነት ፤ በአትላንታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን በክህነትና በስብከተ ወንጌል አገልግለዋል ።

አባ ገብረ ሥላሴ ጥበቡ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስና ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ለስደት ከተዳረጉበት ጊዜ ጀምሮ ፥ ሕጋዊው ቅዱስ ሲኖዶስ ሕገ ቤተ ክርስቲያንን ለማስከበር በሚያደርገው ጥረት በግንባር ቀደምነት የተሰለፉ ፥ የሲኖዶሱን ድምጽ በተለያዩ ሚዲያዎች በማስተላለፍ ፥ በማስተዋወቅ የደከሙ አባት ናቸው ። በስብከት ዘዴ አቀራረባቸውም የሰዎችን ሕይወት በጥልቀት የሚመረምር ሕይወታዊ ትምህርት በማቅረብ እጅግ ተወዳጅ የሆኑ ሰባኬ ወንጌል ናቸው ። በአሁኑ ወቅትም በአንታላንታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ካላቸው የስብከተ ወንጌል ኃላፊነት በተጨማሪ ፥ በቅዱስ ሲኖዶሱ ሥር በተቋቋመው የሰንበት ትምህርት ቤቶች መምሪያ ዋና አስተባባሪ ሁነው እስከአሁን ድረስ በታማኝነትና በትጋት ያገለግላሉ ።
ይህን መንፈሳዊ አገልግሎታቸውን በማየት ፥ በማኅበረ ካህናቱ ፥ በማኅበረ ምእመናኑ ፥ እንዲሁም በሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች ተጠቁመውና ተመርጠው ፥ በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ለከፍተኛው የቤተ ክርስቲያን መዐርገ ክህነት ለኤጲስ ቆጶስነት ተመርጠዋል ።

4ኛ. የመልአከ ሰላም አባ ሳሙኤል ዳኘው አጭር የሕይወት ታሪክ

አባ ሳሙኤል ዳኘው

አባ ሳሙኤል ዳኘው

አባ ሳሙኤል ዳኘው ከአባታቸው ከሊቀ ጠበብት ዳኘው በላይ እና ከእናታቸው ከወይዘሮ አመሁ ታደሰ በ1955 ዓም በቅድስት ሐገር ኢትዮጵያ ተወለዱ ። እድሜያቸው ለትምህርት ሲደርስ በተወለዱበት ደብር ከፊደል እስከ ዳዊት ከመሪጌታ መዝገቡ ለቃል ተምረዋል ። በመቀጠልም የድጓ መምህር ከነበሩት ከመርጌታ በቀለ ምሕረቱ ጾመ ድጓና ምዕራፍ ተምረዋል ። ከዚያም በጎጃም ክፍለ ሀገር በቀራንዮ መድኀኔ ዓለም የቅኔ መምህር ከነበሩት ከመምህር ተስፋ ተገኝ ቅኔ ተቀኝተው እስከ አስነጋሪነት ደርሰዋል ። ቅኔያቸውን ለማስፋት ባላቸው ምኞት ፥ ወደ ጎንጅ በመሄድ በጽላልሽ አማኑኤል ደብር የቅኔ መምህርት ከነበሩትና ብዙ የቅኔ መምህራንን በማፍራት በኢትዮጵያ ሴቶች ታሪክ ታዋቂ ከሆኑት ባለቅኔ ከእመይቴ ገላነሽ ዘንድ በመግባት ቅኔአቸውን አደላድለዋል ።

እርሳቸው ካረፉ በኋላም በዚሁ ደብር የድጓ መምህር ከነበሩት ከመርጌታ ድረስ ሽታ ድጓውን አሂደዋል ። ወደ አቋኋም ቤት በመሄድም በፎገራ ወረዳ በመነጉዘር ኢየሱስ ደብር የአቋቋም መምህር ከነበሩት ከመርጌታ ምሥራቅ ለአራት ዓመት አቋቋም በሚገባ ተምረዋል ። ከዚያም ወደ ዝማሬ መዋሥዕት ቤት በመሄድ በእስቴ ወረዳ በበር ጊዮርጊስ ያስተምሩ ከነበሩትና በርካታ ሊቃውንትን ካፈሩት ከመርጌታ ውብ አግኝ በመሄድ ዝማሬ መዋሥዕት አጠናቀው ተምረዋል ። በመቀጠልም ወደ ባሕር ዳር ከተማ በበዓታ ለማርያም ደብር የቅዳሴ መምህር ከነበሩት ከመምህር አክሊለ ብርሃን ኃይለ ሥላሴ ዘንድ በመግባት ቅዳሴ ተምረው በመምህርነት ተመርቀዋል ።

ታዋቂ ከሆኑት የአገራችን ሊቃውንት የቀሰሙትን ትምህርት ዘመናዊ በሆነ አቀራረብ ማቅረብ እንዲያስችላቸው በማሰብ ፥ ወደ አዲስ አበባ በመምጣት ፥ ቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ገብተው ለሦስት ወራት ለካህናት የሚሰጠውን ኮርስ ተከታትለው የምስክር ወረቀት ተቀብለዋል ። ከዚያም ዓይናማ የቤተ ክርስቲያን ሊቃውንትን በማፍራት ወደሚታወቀው ወደ ሰዋሰወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ ከፍተኛ መንፈሳዊ ት/ቤት ገብተው ለአራት ዓመታት የሚሰጠውን የነገረ መለኮት ትምህርት ተከታትለው በዲፕሎማ ተመርቀዋል ።

አባ ሳሙኤል ዳኘው ፥ መዐርገ ዲቁና የጎጃም ክፍለ ሀገር ሊቀ ጳጰስ ከነበሩት ከብፁዕ አቡነ መቃርዮስ በ1972 ዓ.ም በጎጃም ክፍለ ሃገር በሞጣ ከተማ ተቀብለዋል ። ሥርዓተ ምንኩስና በዝዋይ ሐመረ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ገዳም የተቀሉ ሲሆን ፥ መዐርገ ቅስና ደግሞ፥ በ1986 ዓ ም የመንበረ ፓትርያርክ ቅድስት ማርያም ገዳም የበላይ ኃላፊ ከነበሩት ከብፁዕ አቡነ ሚካኤል ተቀብለዋል ።
አባ ሳሙኤል ዳኘው ፥ ባካበቱት ሰፊ ዕውቀት ቤተ ክርስቲያንን በብዙ አገልግለዋል። በመጀመሪያ በከንባታ ሀድያና ጉራጌ ሀገረ ስብከት የቅዳሴ መምህር ሁነው ለአምስት ዓመታት ያክል አገልግለዋል ።

በመቀጠም ወደ ደቡብ አፍሪካ በመሄድ ፥ በጆሐንስበርግ ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን አስደዳዳሪ በመሆን፥ በአካባቢው አብያተ ክርስቲያናትን በማቋቋም ፥ መጠነ ሰፊ ሥራ ሠርተዋል ። በሕጋዊው ቅዱስ ሲኖዶሱ የመላው አፍሪካ ሊቀ ካህናት በመሆንም፥ በአፍሪካ ሀገሮች እየተዘዋወሩ በማስተማር ስደተኛውን ሕዝብ ለአሥራ አምስት ዓመታት በትምህርተ ወንጌልና በአባታዊ ጉብኝት አጽናንተዋል ።

ወደ አሜሪካ ከመጡበት ጊዜ ጀምሮ በአሁኑ ወቅት ፥ የዴንቨር የዳግሚት ግሸን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያንን በማገልገል ላይ ይገኛሉ ።
አባ ሳሙኤል ዳኘው ለአገልግሎት በተሰማሩበት አካባቢ በሙሉ የፍቅርና የሰላም አባት በመሆን ፥ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ ሕዝቡን በመከራው በኀዘኑ የሚያጽናኑት አባት ስለ ሆኑ በምእመናን ዘንድ እጅግ ተወዳጅ አባት ናቸው ። በስብከተ ወንጌሉ ፥ በቅዳሴው፥ በማኅሌቱ ካላቸው እጅግ ታላቅ ከሆነው ዕውቀት ጋር ትሕትናቸውና አባታዊ አርአያቸው እንዴት ሕዝቡን በፍቅር አንድ አድርጎ እንዳኖረ ፥ በደቡብ አፍሪካና በሌሎችም የአፍሪካ አገሮች ያሉ ምእመናን ምስክር ናቸው ።

በመሆኑም ይህን መንፈሳዊ አገልግሎታቸውን በማየት ፥ በማኅበረ ካህናቱ ፥ በማኅበረ ምእመናኑ ፥ እንዲሁም በሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች ተጠቁመውና ተመርጠው ፥ በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ለከፍተኛው የቤተ ክርስቲያን መዐርገ ክህነት ለኤጲስ ቆጶስነት ተመርጠዋል ።

5ኛ. መልአከ ሰላም አባ ሳሙኤል ተሻገር አጭር የሕይወት ታሪክ

መልአከ ሰላም አባ ሳሙኤል ተሻገር ከአባታቸው ከአቶ ተሻገር ተገኘ እና ከእናታቸው ወ/ሮ ወርቄ ካሳየ በጎንደር ክፍለ ሀገር በእብናት ወረዳ ልዩ መጠሪያ ስሙ ደብረ ይባቤ ገዴ ማርያም በ1945 ዓ.ም ተወለዱ ።

አባ ሳሙኤል ተሻገር

አባ ሳሙኤል ተሻገር

እድሜያቸው ለትምህርት እንደ ደረሰ ፥ ብዙ ሊቃውንትን ካፈሩት ፥ ከመሪጌታ አግማስ / ቆሞስ አባ አበራ ዓለሙ ዘንድ ተልከው ከፊደል እስከ ዳዊት ተምረዋል ። በመቀጠል ቅራረም ኢየሱስ ከመሪጌታ ተሻገር ዘውዴ በመሄድ የግብረ ዲቁና ትምህርት እንዳጠናቀቁ ፥ ከታላቁ ምሁር ከመሪጌታ ጀምበር እና ከልጃቸው ከመሪጌታ ነጋ ጀምበር ፥ አዛሁር ኪዳነ ምሕረት ጸዋትወ ዜማ ማለትም ጾመ ድጓ እና ምዕራፍ ተምረዋል ።
መዐርገ ዲቁናን በ1966 ዓ.ም መጋቢት 29 ቀን በባሕርዳር ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ከብፁዕ አቡነ ማርቆስ ከተቀበሉ በኋላ ፥ ወደ ተወለዱበት ደብር በመመለስ ደብራቸውን በዲቁና ለሁለት ዓመታት አገለገለዋል ። ትምህርታቸውን ለማስፋት ባላቸው ፍላጎት ፥ ወደ ጎጃም ክፍለ ሀገር በመሄድ ደብረ ገነት ኤልያስ ከመሪጌታ ጥበቡ ዜማውን ከከለሱ በኋላ ፥ የቅኔ ትምህርት ከመሪጌታ መሠረት ተምረዋል ። ቅኔያቸውን ለማስፋት ወደ ደንበጫ ቅዱስ ሚካኤል በመሄድ ከመሪጌታ ብዙአየሁ ቅኔያቸውን አደላድለዋል ።

ዘመናዊ ትምህርትን በተመለከተ ፥ መልአከ ሰላም አባ ሳሙኤል ተሻገር በ1972 ዓ.ም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በደብረ ታቦር መንፈሳዊ አዳሪ ትምህርት ቤት በመግባት ፥ የአንደኛና መለስተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን ተከታትለዋል ። በ1977 ዓ.ም ወደ አዲስ አበባ በመምጣት በመንበረ ፀባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በዲቁና እያገለገሉ ፥ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በምሥራቅ አጠቃላይ ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አጠናቅቀዋል ። በመቀጠልም ፥ በብፁዕ አባታችን አቡነ መልከጼዴቅ መልካም ፈቃድና ትእዛዝ በ1983 ዓ.ም ወደ ሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ ከፍተኛ መንፈሳዊ ትምህርት ቤት በመግባት በዚያ የሚሰጠውን ሥርዓተ ትምህርት ተከታትለዋል ። በመቀጠልም ወደ ታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያም የካህናት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት በመግባት በዚያ መዝገብ ቅዳሴ ተምረው በቅዳሴ መምህርነት ተመርቀዋል ።

መልአከ ሰላም አባ ሳሙኤል ተሻገር ፥ በነሐሴ 24 ቀን 1987 ዓ.ም በታላቁ ደብረ ሊባኖስ ገዳም ሥርዓተ ምንኩስናን ተቀብለዋል ፤ በመቀጠልም በ1988 ዓ.ም በመንበረ ፀባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ከብፁዕ አቡነ ጢሞቴዎስ መዓርገ ቅስናን ማዕረገ ቁምስናን ደግሞ ከብፁዕ አቡነ ሚካኤል ተቀብለዋል።

መልአከ ሰላም አባ ሳሙኤል ፥ ቤተ ክርስቲያናቸውን በተለያዩ የኃላፊነት ደረጃዎች አገልግለዋል ። በዚህም መሠረት ወደ አዲስ አበባ ከመጡበት ጊዜ ጀምሮ ፥ በመንበረ ፀባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ፥ በዲቁናና በሊቀ ዲቁና አገልግሎት ለአሥራ ሦስት ዓመታት ፥ በቄሰ ገበዝነት ለአንድ ዓመት አገልግለዋል ። በቅድስት ሥላሴ አንደኛና መለስተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የመጽሐፍ ቅዱስ አስተማሪ በመሆን በመሆን አገልገዋል ። በዚህም ሕፃናት ልጆች በፈሪሃ እግዚአብሔር ታንጸው እንዲያድጉ በማድረግ የሃይማኖት አባትነታቸውን ተግባር ተወጥተዋል ። በዚሁ በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ፥ በገንዘብ ቤት አገልግሎት ለሁለት ዓመት አገልገዋል ።

በ1989 ዓ.ም በብፁዕ አቡነ መልከ ጼዴቅ መልካም ፈቃድ እና ተእዛዝ ሊቀ ካህናት ምሳሌ እንግዳ ባደረጉላቸው ጥሪ መሠረት ወደ ካናዳ በመምጣት ፥ በብፁዕ አቡነ ይስሐቅ እና በሊቀ ካህናት ምሳሌ እንግዳ ፈቃድ በቶሮንቶ መንበረ ብርሃን ቅድስት ማርያም ካቴድራል ረዳት አስተዳዳሪ በመሆን ለአራት ዓመታት አገልግለዋል ። በመቀጠልም በኦቶዋ ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን በአስተዳዳሪነት ለአንድ ዓመት ፥ በካልጋሪ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን በቅስና ለአራት ዓመታት አገልገዋል ።

ከ1997 ዓ.ም ጀምሮ እስከ አሁን ድረስ ለአሥራ አንድ ዓመታት በኤድመንተን ደብረ ሰላም መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን በአስተዳዳሪነት በማገልገል ላይ ይገኛሉ ።

ይህን መንፈሳዊ አገልግሎታቸውን በማየት ፥ በማኅበረ ካህናቱ ፥ በማኅበረ ምእመናኑ እንዲሁም በሰንበት ትምህርት ቤት ተማሪዎች ተጠቁመው ፥ በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ለከፍተኛው የቤተ ክርስቲያን መዐርገ ክህነት ለኤጲስ ቆጶስነት ተመርጠዋል።

6ኛ. የመልአከ ብርሃናት አባ ገብረ ሥላሴ የኋላሸት አጭር የሕወት ታሪክ

መልአከ ብርሃናት አባ ገብረ ሥላሴ (ታደሰ) የኋላሸት በጎንደር ክፍለ ሀገር በደብረ ታቦር አውራጃ በፋርጣ ወረዳ በደብረ ገነት አዛውር ኪዳነ ምሕረት ገዳም ነሐሴ 16 ቀን 1958 ዓ/ም ተወለዱ ።
ዕድሜያቸው ለትምህርት ሲደርስ በትውልድ ቦታቸው ከመጀመሪያው ክፍለ ትምህርት አንሥቶ በየደረጃው ምዕራፉን ፥ ጾመ ድጓውን ፥ ድጓውን ከታወቁት መምህር ከመሪጌታ ጀንበር ወንድም በሚገባ ተምረዋል ።

አባ ገብረ ሥላሴ የኋላሸት

አባ ገብረ ሥላሴ የኋላሸት

የቅኔ ትምህርታቸውንም በደጋ መልዛ ሹምዬ ማርያም ከምትባለው ደብር ከመሪጌታ ፍቅረ ማርያም ተምረዋል ። በተጨማሪም የቅኔ ትምህርታቸውን በሚገባ ለማጠንከር በነበራቸው ፍላጎት ፥ ወደ ታላቁ ደብር ደብረ ታቦር ኢየሱስ በመሄድ ከመሪጌታ ይኄይስ ፈንቴ ቅኔ ከነአገባቡ በሚገባ ተምረዋል ። ወደ አዲስ አበባ በመምጣት የዝማሬና የመዋሥዕት ትምህርታቸውንም በአዲስ አበባ በገነተ ኢየሱስ ቤተ ክርስቲያን ከሊቀ ጠበብት ኅሩይ ለገሠ ተምረዋል ። የቅዱሳት መጻሕፍት ትርጓሜንም ውዳሴ ማርያም ፥ ቅዳሴ ማርያም እና የኪዳን ትርጓሜ ፤ ከሙሉ የቅዳሴ ዜማ ጋር በዚያው በገነተ ኢየሱስ ቤተ ክርስቲያን ከመልአከ ብርሃናት መምህር ተስፋ ወርቅነህ በሚገባ ተምረዋል ።
አባ ገብረ ሥላሴ የኋላሸት ከቤተ ክርስቲያኑ ትምህርትና አገልግሎት ጎን ለጎን ፥ የዘመናዊውን ትምህርት በመከታተል ፥ የአንደኛና መለስተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በአዲስ አበባ የጽጌ በሻህ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ፤ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን ደግሞ በዚያው በአዲስ አበባ በሚገኘው እቴጌ መነን ትምህርት ቤት ተከታተዋል።

የከፍተኛ ትምህርታቸውንም በአሜሪካ ዋሽንግተን ግዛት በሲያትል ቮኬሽናል ኢንስቲቲዩት በቢዝነስ ኮምፒውተር አካውንቲንግ የተመረቁ ሲሆን ፤ በሲያትል ዩኒቨርስቲ የፓስተራል ሊደር ሽፕ እና ካውንስሊንግ ትምህርታቸውን ተከታትለዋል ።

አባ ገብረ ሥላሴ የኋላሸት ፥ መዐርገ ዲቁናን ከብፁዕ አቡነ እንድርያስ የጎንደር ሀገረ ስብክት ሊቀ ጳጳስ የተቀበሉ ሲሆን ፤ ሥርዓተ ምንኩስናን እና መዐርገ ቅስናን ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ እጅ ተቀብለዋል ።

አባ ገብረ ሥላሴ የኋላሸት ቤተ ክርስቲያን ከልጅነት እስከ እውቀት ባስተማረቻቸው እና ባገኙት ሰፊ የሥራ ልምድ ቤተ ክርስቲያንን በተለያዩ ኃላፊነቶች አገልግለዋል ። ከእነዚህም መካከል ፥ ባደጉበት ደብር በዲቁና ፣ እንዲሁም በአዲስ አበባ ገነተ ኢየሱስ ቤተ ክርስቲያን በዲቁና ፥ በሊቀ ዲቁና ፥ በዋና ጸሐፊነትና በሰንበት ትምህርት መምህርነት ፣ በአዲስ አበባ መንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በዲቁናና፥ በሊቀ ዲቁና ። በናይሮቢ ኬንያ በሚገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በዲቁና ፥ በሊቀ ዲቁና ፥ በዋና ጸሐፊነትና በሰንበት ትምህርት ቤት መምህርነት ፤ በኦክላንድ መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን በዲቁና ፤ በሲያትል ዋሽንግተን ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ደግሞ በሊቀ ዲያቆንነት ፥ በዋና ጸሐፊነት ፥ በሰንበት ትምህርት ቤት መምህርነት ያገለገሉ ሲሆን ። በአሁኑ ወቅት ደግሞ የገዳሙ አስተዳዳሪ በመሆን በማገልገል ላይ ይገኛሉ ።
ይህን መንፈሳዊ አገልግሎታቸውን በመመልከት ፥ በማኅበረ ካህናቱ ፥ በማኅበረ ምእመናኑ እንዲሁም በሰንበት ትምህርት ቤት ተማሪዎች ተጠቁመው ፥ በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ለከፍተኛው የቤተ ክርስቲያን መዐርገ ክህነት ለኤጲስ ቆጶስነት ተመርጠዋል።

ስብሐት ለእግዚአብሔር በሰማያት ይቆየን ።

በአውሮፓ የኢትዮጵያውያን ኮንፍረንስ EFE Conference

$
0
0

Ethiopian Forum in Europe conference

Federalism and the Nattional Question in Ethiopia

20160627_080713

 

 

የሕዝብን መብት የማያከብር መንግሥት በሕዝብ አመፅ ይወገዳል

$
0
0
የኢትዮጵ ሕዝ የጋራ ግል ሸን (ሸን)
Ethiopian People’s Congress for United Struggle (Shengo)
www.ethioshengo.org shengo.derbiaber@gmail.com
ሐምሌ 6 ቀን 2008 . ም ጁላይ 13, 2016
የሕዝብን መብት የማያከብር መንግሥት በሕዝብ አመፅ ይወገዳል
ላለፉት ሃያ አምስት ዓመታት ሥልጣኑን በጉልበት ወስዶ፣የሕዝቡንመብትገፎ፣ያገሪቱን
ሃብትና ንብረት የሚዘርፈው ቡድን ሥልጣኑና አድራጎቱ ዝንተዓለማዊእንደማይሆን
ከወደቁትና ከተወገዱት ተመሳሳይ መንግሥታት ታሪክ ገና አልተማረም። ከፋፍዬ
እኖራለሁየሚለውስልቱእየተጋለጠበየአቅጣጫውበሕዝብተቃውሞእየተዋከበይገኛል።
ወደ ታሪክ መቃብር የሚገባበት ቀን እያጠረ መጥቷል። አሁን በጎንደር ቀደም ሲል
በሸዋ,በተለያዩያኦሮሚያክልልአካባቢወችበጋምቤላናበሌሎቹምያገሪቱክፍሎች
የተነሳው ሕዝባዊ አመፅይህንየሚያመላክቱናውድቀቱንየሚያፋጥኑተቃውሞዎች
ናቸው።

Amhara Idintity Committee Discussion in Gonder

በማስፈራራትና በዛቻ የሕዝብ ትግል አይቆምም

$
0
0

ቢሆን ይሆናል ባይሆን አይተነው፣

እንሄዳለን አደባይተነው።

በዚህ አይነቱ ስንኝ የታጀበ የእልቂት ፉከራና ዛቻ አባይ ጸሃዬና ስዩም መስፍን የተባሉት ቀንደኛ የሕወሀት

ወንጀለኞች በብዙሃን የመገናኛ መድረክ ላይ ከ40 ደቂቃ በላይ በሰጡት ማብራሪያ የተደመጠ የሰሞኑ

የሽብር መልእክት ነበር።እነዚህ የሕዝብና የአገር ጠላቶች ድርጅታቸው በሚመራው መንግሥት ላይ

የደረሰውን የፖለቲካና ማህበራዊ ክስረት ተመርኩዘው ካደረባቸው ስጋት በመነሳት ሕዝቡን ያልነቃ፣ዃላ

ቀርና ለውጭ ሃይሎች ያጎበደደ ያቀጣጠለው ግርግር ነው ብለው የስድብና የንቀት ናዳ ሲያወርዱበት፣

የሕዝቡን እሮሮ የሚያጋልጡትንና የሚታገሉትን በውስጥና በውጭ የሚገኙትን የለውጥ ሃይሎችን

እንደማንኛውም አምባ ገነን ስርዓት ጥላሸት እያለበሱ ከጥያቄው ለማምለጥ ሲውተረተሩ ተደምጠዋል ።

የነፍጠኞች፣ የትምክህተኞች፣የጠባቦችና የውጭ አገር ሴራ አስፈጻሚዎች በማለት ከሰዋል።በዚህም ብቻ

አላቆሙም እራሳቸውን የአንድነት፣የሰላም፣የእድገት፣ የእኩልነት፣የዴሞክራሲ ጠበቃና ፈጣሪዎች እንደ

ሆኑ አድርገው አቅርበዋል። እነሱን መቃወም ማለት ደግሞ ሰላም ማናጋት፣እድገትን መጎተት፣አንድነትን

ማፍረስ፣እኩልነትን ሽሮ አንዱ ጌታ ሌላው ባሪያ የሚሆንበትን ስርዓት መልሶ ለማምጣት የሚደረግ

አድማና ሴራ ነው በማለት ጥፋቱን ከራሳቸው ላይ አውርደው በሌላው ላይ ለመጫን ሞክረዋል።ለመሆኑ

እድገት ሲባል የሕዝብ አስተያየትንና ንቃትን ያካተተ አይደለምን? ሕዝቡን ዃላ ቀር፣ደደብ ብለው

ከተሳደቡ በሕዝቡ ንቃት ለውጥ አልመጣም ማለት ነው።

%e1%88%98%e1%8c%8d%e1%88%88%e1%8c%ab-%e1%89%81-1

Demonstration Against Ethiopian Government Ottawa Canada

$
0
0

Demonstration Against Ethiopian Government Ottawa Canada

Yes


Radio Show For October 23/2016

$
0
0

EMF Website Editor Journalist Kinfu Asefa

and more

 

Radio Show For Describer 11/2016

A Look At The Ethiopian Political Discourse : Radio Show, January 8, 2017

$
0
0

Abrha Belai, Fekade Shawakena, Kassa Ayalew and Addis Dimts Radio host Abebe Belew look at the Ethiopian Political discourse.

Listen to Addis Dimts special discussion about the growing political challenges facing Ethiopia and proposed changes that are needed to win democracy and freedom in Ethiopia.

Addis Dimts Radio about Shamebel Zwedu Ayalew and more

Radio Show For April 9/2017

$
0
0

Habetamu Ayalew Frist Public Appearance In DC

Habtamu Ayalew Shares His First Hand Experience about Human Rights Violations in Ethiopia

Radio Show For May 7/2017

$
0
0

Addis Dimts Radio May 7 Watch Video


የኢትዮጵያ ህዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ(ሸንጎ)አራተኛ ጉባኤውን ከኦገስት 18-20 ድረስ

$
0
0

 

Watch “የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ August 20 2017” on YouTube

Ethiopian People’s Congress For United Struggle (Shengo )4th Convention Part 1

$
0
0

“የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ (ሸንጎ) አራተኛ ጉባዔውን በተሳካ ሁኔታ አጠናቀቀ” Part 1

 

Ethiopian People’s Congress For United Struggle (Shengo )4th Convention Part 2

Radio Show For October 8/2017

$
0
0

Radio Show For October 8/2017

 

ESAT Yetsehafian Demitsoch Reeyot with Geletaw Zeleke Thur 2 Nov 2017

Viewing all 96 articles
Browse latest View live